አዲስ ዘመን ቅዳሜ መጋቢት 20 ቀን 2017ዓ.ም
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ ገንዘብ ቢሮ የምስ/ጐጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ የግዥና ንብ/አስ/ቡድን አገልግሎት ለሚሰጣቸው ሴ/መ/ቤቶች
አገልግሎት የሚውል ሎት 1 የመኪና ጎማ ከነካለማንዳሪው ሎት 2. የውጭ ፈርኒቸር እቃ ሎት 3. የስፖርት ትጥቅ በድጋሚ የወጡሎቶች
ማለትም.ሕንጻ መሳሪያ ሎት2.የአፈር ምርምር ኬሚካል እና የላቦራቶሪ እቃዎች ሎት 3. በኮንትራት ውል የሚያዝ የማሽነሪ መለዋወጫ
እቃዎች ሎት 4. የእጽዋት ዘር ላብራቶሪ እቃዎች ሎት እና 5.የኮምፒውተርና ተዛማጅ እቃዎች ሎት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት
ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾቾ መወዳደር የሚችል መሆኑን ይጋብዛል፡፡
1. ዘርፉ የተሰማሩ ህጋዊ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉና ፈቃዳቸውን ያሳደሱ ማስረጃ
ማቅረብ የሚችሉ፣
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ቲን ነምበር ያላቸውና ማቅረብ የሚችሉ።
3. የግዥው መጠን ከብር 200,000.000 /ሁለት መቶ ሺህ በላይ/ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ
/VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተቁ 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ
ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው ::
5. በተጫራቾች የሚቀርበው የመወዳደሪያ ዋጋ ለ40 ቀን ፀንቶ የሚቆይ መሆን አለበት፡
6. የሚገዙት ዕቃዎችን /አገልግሎቶች አይነትና ዝርዝር መግለጫ ስፔስፊኬሽን/ ከመጫረቻ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ በምስ/ጐ/
ዞን/አስ/ገ/ፅ/ቤት በተከፈተው የአባይ ባንክ አካውንት ቁጥር 2052117320503019 ወይም ለምስ ጐጃም ዞን ገ/ኢ/ት/መምሪያ
በተከፈተው በኢትዮጵያ የንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000335896158 በመክፈል ከግዥና ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በመቅረብ
የጨረታ ሰነዱን ማግኘት ይችላሉ::
8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ሎት 1 የመኪና ጎማ ከነከለመዳሪው
10,000 /አስር ሺህ ብር ሎት 2. የውጭ ፈርኒቸር 5,000 /አምስት ሺህ ብር ሎት 3 ህንጻ መሳሪያ 1,000 /አንድ ሺህ
ብር/ ሎት 4 የአፈር ምርምር የኬሚካል እና የላብራቶሪ እቃዎች 4000 /አራት ሺህ ብር/ 5. የማሽነሪ መለዋወጫ እቃዎች
15,000 አስራ አምስት ሺህ ብር/ 6 የእጽዋት ዘር የላብራቶሪ እቃዎች 3,000 /ሶስት ሺህ ብር/ 7. የስፖርት ትጥቅ
5,000 አምስት ሺህ ብር 8. የኮምፒውተርና ተዛማጅ እቃዎች ሎት 25,000 /ሃያ አምስት ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ
ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ አለባቸው።
9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በገንዘብ መምሪያ በግዥና
ንብ/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 01 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ
ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን የጨረታ ሰነድ መግዛትና የመወዳደሪያ ሃሳብ ሞልቶ እስከ 4:00 ሰዓት ማስገባት ይችላሉ፡፡
የጨረታ ሳጥኑም በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ
4:30 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም መምሪያው ጨረታውን የሚከፍት መሆኑን እንዲታወቅ፣ ሆኖም
የጨረታው መክፈቻ ቀን የበዓላት ቀን ወይም የካላንደር ዝግ ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
10. የጨረታ ሰነድ ስርዝ ድልዝ መሆን የለበትም ስርዝ ድልዝ ከሆነም ፓራፍ መደረግ አለበት ኮሬክሽን ፍሉድ
መጠቀም ከጨረታ ውድድር ውጭ ያደርጋል፡፡
11. ተጫራቾች መ/ቤቱ ካዘጋጀው የስራ ዝርዝር/ስፔስፊኬሽን/ ውጭ መጨመርም ሆነ መቀነስ ከጨረታ ውድድር
ውጭ ያደርጋል፡፡
12 በሌሎች ተጫራቾች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ከጨረታ ውጭ ያደርጋል፣
13. የስፖርት ትጥቅ በተመለከተ መ/ቤቱ በሚያቀርበው ናሙና መሰረት ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፡፡
14. አሸናፊ የሚለየው በሎት ጥቅል ድምር ውጤት ዝቅተኛ ዋጋ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ የጨረታ ሰነድ ዝርዝር ላይ
ዋጋ መሙላት አለበት፡፡ የጨረታ ሰነድ ዝርዝር ላይ ዋጋ ሙሉ ለሙሉ አለመሙላት ከጨረታ ውጭ ያደርጋል።
15. ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ወይም ውል የያዙባቸውን እቃዎች/አገልግሎቶች በምስ/ጎ/ዞን መምሪያዎች ባሉ
የፑል ንብረት ክፍሎች ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
16. የጨረታ መዝጊያ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የማወዳደሪያ ሃሣብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ
ማድረግና ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም
17. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን መሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፤
18. አሸናፊው ተጫራች ማሸነፉ ከተገለጸበት ጊዜ ጀምሮ 5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት
ውስጥ ውል መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
19. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ምስ/ጐጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ በአካል
በመቅረብ ምስ ጐጃም ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት ህንጻ 1ኛ ፎቅ ወይም
በስልክ ቁጥር፡-05877713158 ደውስው መጠየት ይችላሉ፡፡
በአብክመ ገንዘብ ቢሮ የምስ/ጎጃም ዞን ገንዘብ መምሪያ ግዥና ንብ/አስ/ ቡድን