አዲስ ዘመን ቅዳሜ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም
የጨረታ ማስታወቂያ
በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ተይዘው የተወረሱ የተለያዩ
ኮስሞቲክስ ዘርፍ ዕቃዎች፣ አልባሳት ዘርፍ እቃዎች፣ የንጽህና መጠበቂያ ዘርፍ እቃዎች፣ ኤልክትሮኒክስ ዘርፍ እቃዎች፣ ልዩልዩ ዘርፍ እቃዎች እና ስፔርፓርት ዘርፍ እቃዎች በሀራጅ ጨረታ በጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 25/2018
ዓ.ም እቃዎቹን ባሉበት ሁኔታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም፡-
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን
እንገልጻለን፡፡
1. በጨረታው ሽያጭ ስርዓት ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች በዘርፉ የጸና የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣
የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር እና የዘመኑን ግብር የከፈለ ስለመሆኑ
ከግብር ሰብሳቢ መስሪያ ቤት የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ ያለበት ሲሆን በሀራጅ ጨረታ ለሚወዳደሩባቸው እቃዎች ከላይ የተጠየቁትን መረጃዎች በጨረታ መክፈቻ ቀን ይዘዉ መቅረብ አለባቸው፡፡
2. ከላይ በተራ ቁጥር አንድ የተገለጸው ቢኖርም ግምታዊ ዋጋው ከብር 500 ሺህ በታች የሆነ ማንኛውም እቃ
ለመግዛት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርትፍኬት ማቅረብ አያስፈልግም እንዲሁም የሚሸጠው እቃ ተሽከርካሪ ሲሆን የተሽከርካሪው አስመጪ ወይም ባለቤትና ቤተሰብ ከሆነ ሰው በስተቀር ማንኛውም እድሜው
ከ 18 ዓመት በላይ የሆነ ኢትዮጲያዊ ቅድመ ሁኔታዎቹን ማሟላት ሳያስፈልገው በጨረታው ሊሳተፍ ይችላል፤
3. በሀራጅ ጨረታ ለወጡት እቃዎች ለመሳተፍ ለምድብ 1 ኮስሞቲክስ ዘርፍ ዕቃዎች ብር200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር)፤ ለምድብ 2 አልባሳት ዘርፍ እቃዎች ብር 51,000 (ሃምሳ አንድ ሺህ ብር)፣ ለምድብ 3 አልባሳት ዘርፍ
እቃዎች ብር 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር)፣ ለምድብ 4 ልዩልዩ ዘርፍ እቃዎች ብር 15,500 (አስራ አምስት ሺህ
አምስት መቶ ብር)፣ ለምድብ 5 ንጽህና መጠበቂያ ዘርፍ እቃዎች ብር50,000(ሃምሳ ሺህ ብር)፣ ለምድብ 6 ኤልክትሮኒክስ ዘርፍ እቃዎች ብር 50,000(ሃምሳ ሺህ ብር)፤ ለምድብ 8 ስፔርፓርት ዘርፍ እቃዎች ብር 5,000
(አምስት ሽ ብር) እና ሰምድብ 9 ልዩልዩ ዘርፍ እቃዎች ብር 50,000(ሃምሳ ሺህ ብር) ለየብቻው የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO በቀጥታአካው ንት ቁጥር
1000296553216 በጋላፊ ጉምሩክ ቅርንጫፍ
ጽ/ቤት ስም በማሰራት የጨረታ ሰነዱንእና በተራ ቁጥር አንድ የተገለጹትን መረጃዎች በመያዝ በቀን 4/0/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ላይ መገኘት አለባቸው፡፡
4. ከላይ በተራ ቁጥር 3 በተገለጸው መሰረት በቂ የጨረታ ማስከበሪያ ያላስያዘ ተጫራች መወዳደር ወይም መጫረት አይችልም፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ እና ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡00 6፡00 ሰዓት ከሰዓት በኋላ ከ9፡00-12፡00 የእቃዎቹን ዝርዝር የያዘ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር)
በመክፈል ይህ ጨረታ ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ
4/10/2018 ጠዋት 3፡00 ድረስ በውርስ መጋዘን አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 08 መግዛት ይችላሉ፡፡
6. ለጨረታ የሚቀርቡ ዕቃዎች ለናሙና ዕይታ የሚቀርቡበት ጊዜ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ግንቦት 29/2018
ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 4/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ድረስ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ጠዋት 2፡00-6፡30
ሰዓት ከሰዓት በኃላ ከ9፡00-12፡00 ሰዓት እና ቅዳሜ ጠዋት 2፡00-6፡00 ሰዓት የእቃዎቹን ዝርዝር መመልከት ይችላሉ፡፡
7. ተጫራቾች በሚከተለው የጨረታ የጊዜ ሰሌዳ (ስኬጁል) መሠረት መጫረት ይችላሉ፡፡
|
ተ.ቁ
|
የቅ/ጽ/ቤቱ ስም
|
የጨረታው
አይነት
|
የንብረት መመልከቻ ቀን
የጨረታው ማስታወቂያ
በጋዜጣ ከወጣበት ቀን
ጀምሮ
|
የጨረታው መዝጊያ እና መክፈቻ
ቀንና ሰዓት
|
|
1
|
ጋላፊ ጉምሩክ
ቅ/ጽ/ቤት
|
ሀራጅ
ጨረታ
|
እስከ
4/10/2018
ከጠዋቱ 3፡00 ድረስ
|
በ4/10/2018
ዓም ከጠዋት 3፡00
ሰዓት ይከፈታል
|
8. የጨረታው መክፈቻ ቦታ፡- በጋላፊ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የሚካሄድ ሲሆን ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በቦታው ባይገኙም የጨረታ
ሰነዱ በታዛቢዎች ፊት ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች በተራ ቁጥር አንድ የተጠቀሱ ማስረጃዎች ኦርጂናል ይዘው
መቅረብ አለባቸው፡፡
9. በጨረታ ለሚሸጥ እቃ የጨረታ ውጤት እንደተገለጸ ከአሸናፊው ጋር የሽያጭ ውል እንደተደረገ ይቆጠራል፡፡
10. ምድብ ለወጣላቸው ሀራጅ እቃዎች ጨረታው የሚካሄደው በምድብ ሲሆን ተጫራቾች አሸናፊ የሚያደርጋቸው ለምድቡ ባቀረቡት የእያንዳንዱ እቃዎች ዋጋ ድምር ከፍተኛው ዋጋ ይሆናል፡፡ በተጨማሪም ተጫራቾች በምድቡ ለቀረቡት ለእያንዳንዱ እቃዎች ዋጋ መስጠት አለባቸው፡፡
11. ተጫራቾች ከአሸነፉበት የእቃ ዋጋ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ (5%) የሚጨመር ይሆናል።
12, ተጫራቾች ያስያዙትን የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) በተመለከተ ለአሸናፊው ተጫራች ካሸነፉት የዕቃ ዋጋ ላይ የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ውጤቱ በተገለጸ በ3 (ሶስት) ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
13. አሸናፊው ተጫራች ዕቃዎቹን ባሉበት ቦታ እና ሁኔታ የመረከብ እና ለማጓጓዝ የሚያስፈልጉ ወጪዎችን ሁሉ
ራሱ ይችላል፡፡
14, አሸናፊ ተጫራች ማሸነፋቸውን በደብዳቤ ከተገለጸላቸው ቀን ጀምሮ በዐ5 (በአምስት) ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን
እቃ ዋጋ ገቢ በማድረግ እቃውን መረከብ ያለበት ሲሆን ይህን ባይፈጽም ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት (CPO)
ለመስሪያቤቱ ገቢ ተደርጎ ዕቃው በድጋሜ ለጨረታ የሚቀርብ ሲሆን ነገር ግን አሸናፊው የአሸነፈበትን የእቃ
ዋጋ ገቢ አድርጎ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ እቃውን ያላነሳ እንደሆነ ለሚቆይበት ተጨማሪ ጊዜ የመጋዘን ኪራይ የሚከፍል ይሆናል፡፡ ሆኖም እቃውን በሁለት ወር ውስጥ ካላወጣ ለንብረቱ የተከፈለው ዋጋ ለመስሪያቤቱ ገቢ
ሆኖ እቃው እንደተተወ ተቆጥሮ በሽያጭ ይወገዳል፡፡
15. በጨረታ የሚሸጠው እቃ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከመወረሱ በፊት የእቃው አስመጪ ወይም ባለቤትና ቤተሰብ
የነበሩ ሰዎች በጨረታዉ መሳተፍ አይችሉም፡፡
16. ለጨረታ የቀረቡት እቃዎች የሚገኙበት ቦታ ጋላፊ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት መሆነ ይታወቅ፡፡
17. ኮሚሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ውርስ መጋዘን አስተደደር የስራ ሂደት ስልክ ቁጥር 033 559 0114 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በጉምሩክ ኮሚሽን የጋላፊ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት